ኢትዮጵያ በዘርፉ ስኬታማ የስድስት ወር አፈጻጸም እንዳስመዘገበች የግብርና ባለስልጣን አስታውቋል።
የስጋ ምርቷን ወደ ጎረቤት ሀገራት እና መካከለኛው ምስራቅ ብቻ ትልክ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን የሩቅ ምስራቅ ሀገራትን መድረስ እንደቻለች ተገልጿል።
ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት ቻይና እና ሞንጎሊያ ድረስ የተቀቀለ ስጋ መላክ መጀመሯን የግብርና ባለስልጣን አስታውቋል።
ባለፈው ስድስት ወር ወደ ውጭ የተላከው የቁም እንሰሳት በ2016 ዓ.ም ሙሉ ዓመት ከተላከው የ100 ሺህ ብልጫ ያለው ሲሆን በገቢ ረገድ የ10 ሚሊዮን ዶላር ልዩነት እንዳለው የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።